EMSA – Yetenaweg and Engender Health https://srhr.yetenaweg.com Sexual and Reproductive health and rights (SRHR) in Ethiopia Sat, 24 Feb 2024 11:15:08 +0000 en-US hourly 1 https://wordpress.org/?v=6.7.1 https://srhr.yetenaweg.com/wp-content/uploads/2024/01/yetenawegfinallogo-1-150x150.png EMSA – Yetenaweg and Engender Health https://srhr.yetenaweg.com 32 32 የመጀመሪያዎቹ 1000 ቀናት https://srhr.yetenaweg.com/%e1%8b%a8%e1%88%98%e1%8c%80%e1%88%98%e1%88%aa%e1%8b%ab%e1%8b%8e%e1%89%b9-1000-%e1%89%80%e1%8a%93%e1%89%b5/ Thu, 03 Feb 2022 09:27:30 +0000 https://yetenaweg.com/?p=2613 (በፍሰሀ ሙሉጌታ Myungsung Medical college የህክምና ተማሪ-C1)

የመጀመሪያዎቹ 1000 የህይወት ቀናት ማለት በሴት ልጅ እርግዝና እና በልጇ ሁለተኛ    ልደት መካከል ያሉት ቀናቶች ናቸው፡፡   ይህም ጊዜ  ለሙሉ ጤና እና እድገት መሠረት  የሆነ   ነው።          በዚህ ጊዜ ውስጥ የልጁ አመጋገብ እና እንክብካቤ ህይወቱን ጤናውን ለመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በልጁ  እድገት እና የመማር ችሎታ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራል፡፡ በዚህ ጊዜ አእምሯችን ከሌሎች ዕድሜ ክልሎች በበለጠ ፍጥነት ያድጋል። ስለዚህ ለልጁ ተገቢውን ንጥረ ነገር መመገብ በጣም አስፈላጊ ነው::

የመጀመሪያዎቹ 1000 ቀናት በ 3 ይከፋላሉ:-

1. የእርግዝና ጊዜ (0-9 ወር)

2. Infant (0-1 አመት)

3. Toddler (1-2 አመት)

1,የእርግዝና ጊዜ (0-9 ወር)

በእርግዝና ወቅት አዕምሮ በፍጥነት ማደግ ይጀምራል:: በእርግዝና የመጀመሪያ ወር መጨረሻ ላይ ፅንሱ 10,000 ነርቮች እንዳሉት ይገመታል፣በ 6ተኛው ወር መጨረሻ 10 ሚሊዮን ይደርሳል።፡ በዚህ ጊዜ ፅንሱ ከእናቱ የሚያገኘው ንጥረ ነገሮች  ነርቮቹን የመፍጠር ሂደት ላይ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ፡፡ በዋነኝነት  አይረን፣ፕሮቲን፣ኮፐር፣ ፎሌት፣ ዚንክ ፣ አዮዲን እና ቅባቶች ናቸው፡፡ እነዚህንም ለማግኘት የሚከተሉትን ምግቦች ቢመገቡ ይመረጣል፡-

1. አትክልቶች እና ፍራፍሬዎች

2. ሥጋ

3. ምስር

4. አቮካዶ

5. የዱባ ፍሬ

6. የወተት ምርቶች

7. ስፒናች

8. ሰላጣ

9. ስኳር ድንች

በተቃራኒው እርግዝና ወቅት ከሚከተሉት ምግቦች መራቅ ይመከራል:-

1. ቱና እና ማርሊንን ጨምሮ ከፍተኛ የሜርኩሪ ዓሳን ያስወግዱ።

2. ያልበሰል ስጋ፣እንቁላል

3. ምንም እንኳን ጉበት ስጋ ጥሩ የቫይታሚን ኤ፣ቫይታሚን ቢ12፣ እና ፎሌት ምንጭ ነገር ግን ከመጠን በላይ ቫይታሚን ኤ መመገብ ፅንሱን ሊጎዳ ይችላል። ስለዚህ የሚበላውን መጠን ይገድቡ ፡፡

4.ፍራፍሬዎችና አትክልቶች ቶክሶፕላዝሞሲስ በተባሉ ተውሳኮች ሊበከሉ ይችላሉ፡፡ ሁሉንም ፍራፍሬዎችን እና አትክልቶችን በንጹህ ውሃ ማጠብ አስፈላጊ ነው፡፡

5. ሁሉንም የአልኮል ዓይነት ያስወግዱ፡፡ አልኮል መጠጣት የፅንስ መጨንገፍ እና የአእምሮ ዘገምተኝነትን ያስከትላል፡፡

2, Infant (0-1 አመት)

ሕፃን ልጅ ከተወለደበት ጊዜ አንስቶ እስከ አንድ አመት ድረስ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ልክ በእርግዝና ጊዜ አመጋገብ ትልቅ ሚና እንደሚጫወተው በዚህም ጊዜ ወሳኝ ነው፡፡

ልጁ በዚህ ጊዜ ሊወስዳቸው ከሚገባቸው ምግቦች አንዱ እና ዋነኛው የጡት ወተት ነው፡፡ የአሜሪካ የሕፃናት ሕክምና ማህበር ለመጀመሪዎቹ 6 ወራት ጡት ማጥባት ብቻ ያለ ምንም ተጨማሪ ምግብ እና መጠጥ ይመከራል፡፡ ከዚያም በተጨማሪ ለ 1 አመት ያህል ከምግብ እና ፈሳሽ ጋር ጡት ማጥባት ተገቢ ነው፡፡  በቀን እስከ 20 ጊዜ ጠዋት እና ማታ ያጥቡ፡፡

 

ጡት ማጥባት ህፃኑን ብቻ ሳይሆን የሚጠቅመው እናቶችንም ከጡት እና ከማህፀን ካንሰር ለመከላከል ይረዳል፡፡

ምግብ ሲጀምሩ የሚከተሉትን ነገሮች አስተውሉ፡-

1. በመጀመሪያ አንደኛውን ጡት ሙሉ በሙሉ ባዶ ማድረግ ከዚያም ወደሌላኛው ጡት ይሂዱ። ይሄ ህፃኑ የሚቻለውን ያህል ንጥረነገር እንዲያገኝ ያግዛል፡፡

2. ልጅዎ ቢታመም በቀን የሚጠባበትን ቁጥር ይጨምሩ፡፡

3. ከወሊድ በኋላ ባሉት 45 ቀናት ውስጥ የቫይታሚን ኤ ታብሌቶች ወይም ምግቦችን ይውሰዱ፡፡

4. ልጅዎን በቀን ከ20-30 ደቂቃዎች የፀሀይ ብርሀን ያሙቁ፡፡

5. ምግብ በሚጀምሩበት ጊዜ ለልጅዎ በአንድ ጊዜ አንድ አዲስ ምግብ ብቻ ይስጡት – ድብልቅ ሳይሆን (እንደ ጥራጥሬ እና ፍራፍሬ ወይም ስጋ)። ሌላ አዲስ  ምግብ ከመጨመርዎ በፊት አዲሱን ምግብ ከ 3 እስከ 5 ቀናት በተከታታይ ይስጡት፡፡ በዚህ መንገድ ልጅዎ ለምን አይነት ምግቦች አለርጂክ ሊሆኑ እንደሚችሉ ማወቅ ይችላሉ።

6. በትንሽ መጠን አዲስ ምግብ ይጀምሩ – መጀመሪያ ላይ አንድ የሻይ ማንኪያ እና ቀስ በቀስ ወደ አንድ የሾርባ ማንኪያ ከፍ ያድርጉ።

7. በደረቅ የሩዝ እህል ይጀምሩ ከዛ አትክልቶች ፣ ፍራፍሬዎች እና ከዚያም ስጋዎች ይመገቡ፡፡

8. በቤት ውስጥ የተሰሩ የህጻናት ምግቦችን በምታዘጋጁበት ጊዜ ጨው ወይም ስኳርን አይጠቀሙ፡፡ የታሸጉ ምግቦች ከፍተኛ መጠን ያለው ጨው እና ስኳር ሊይዙ ስለሚችሉ ለህጻናት ምግብ መዋል የለባቸውም። ለተገቢ ያልሆነ ውፍረት ያጋልጣሉ፡፡

9. የላም ወተት ከ1 አመት በፊት መጀመር የለበትም፡፡

10. ሁልጊዜ ፍራፍሬዎችን እና አትክልቶችን ይጠቡ፣ ይላጡ እና ፍሬውን ያስወግዱ።

11. ከመሬት ጋር የሚገናኙ ፍራፍሬዎች፣ አትክልቶች እና ማር ላይ ልዩ ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡ የምግብ መመረዝን የሚያስከትሉ የ ቦቱሊዝም(botulism) ንጥረ ነገሮችን ሊይዙ ይችላሉ፡፡ እስከ 1 አመት ድረስ ልጆች ማር መመገብ የለባቸውም፡፡

 

3,Toddler (1-2 አመት)

ህፃናት ልጆች እንዲያድጉ እና ተገቢ የሆነ የክብደት መጠን እንዲያገኙ  በፕሮቲን የበለጸጉ ምግቦችን ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ስንዴ፣ ስኳር የሌለው ወተት እና ሌሎች የወተት ተዋጽኦዎች ያስፈልጋቸዋል፡፡ በዚህ ጊዜ የቅባት እና የስኳር መጠንን መመጠን አስፈላጊ ነው፡፡ የክብደት መጠን መጨመር በወደፊት ህይወት ላይ ለአላስፈላጊ በሽታዎች ይዳርጋል፡፡

የልጆች ባህሪን ለመቆጣጠር ምግብን ከመጠቀም ይልቅ የራሳቸውን ምግብ መጠን እንዲቆጣጠሩ መፍቀድ ይመከራል። ልጆች ወላጆቻቸውን እና ሞግዚታቸውን ይመለከታሉ፡፡ ስለዚህ አንድ ወላጅ ጤናማ ምግብ ሲመገብ ልጆቹም እንዲመገቡ ያነሳሳቸዋል።

ልጅዎ በቀን ግማሽ ሊትር ወተት ማግኘት አለበት፡፡ ይህም በቂ ካልሺየም፣ ቫይታሚን ዲ እና ስብ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል፡፡

1. ልጅዎ ከሁሉም የምግብ ዓይነቶች ማለትም ከአትክልቶች፣ ፍራፍሬዎች፣ ፕሮቲኖች፣ ጥራጥሬዎች እና የወተት ተዋጽኦዎች ምግብ ማግኘት አለበት።

2. ልጅዎን ጡጦ ሳይሆን ኩባያ እንዲጠቀም ያበረታቱት።

3. ሹካ/ማንኪያ መጠቀምን ጨምሮ የጠረጴዛ ስነምግባርን ማስተማር መጀምር

4. ታገሱ! ህፃናት አንድን ነገር አንድ ቀን መውደድ እና በሚቀጥለው ጊዜ መብላት እንደማይፈልጉ በመወሰን መራጭ ተመጋቢዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ከሁሉም     ምግቦች ትንሽ ክፍሎች ያቅርቡ እና የምግብ ሰዓቱን አስደሳች ያድርጉት! የተለያየ ጣዕም ያላቸው ባለቀለም ምግቦችን ያቅርቡ። ዛሬ ምግብን እምቢ ቢሉም     ማገልገልዎን ይቀጥሉ እና እንዲሞክሩ ያበረታቷቸው፤ነገር ግን እንዲበሉ አያስገድዷቸው፡፡

5. መላው ቤተሰብ አንድ ላይ ቢመገብ ፤አንድ አይነት ምግብ ይመገቡ፤ በዚህ ተነሳስቶ ህጻኑም ተመሳሳይ ምግብ ይመገባል፡፡

6. ለልጅዎ በቀን ሶስት መደበኛ ምግቦች እና 2 መክሰስ ያቅርቡ፡፡

References

1. American Academy of Pediatrics

2. NUTRITION IN THE FIRST 1,000 DAYS: A Foundation for Brain Development and Learning. (n.d.).     Retrieved from https://thousanddays.org/.

3. Health, F. D. (2006). Complementary Feeding Recipes for Ethiopian Children 6-23 Months Old.

  • https://www.stanfordchildrens.org/en/topic/default?id=feeding-guide-for-the-first-year-90-P02209. (n.d.). Retrieved from https://www.stanfordchildrens.org.

 

ይህ ፅሁፍ በዶ/ር ትንሳኤ አለማየሁ (የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት/የተላላፊ በሽታዎች ሰብ ስፔሻሊስት) እና የጤና ወግ ኤዲተሮች የተገመገመ ነው።

]]>
የእናቶች ሞት በኢትዮጵያ https://srhr.yetenaweg.com/%e1%8b%a8%e1%8a%a5%e1%8a%93%e1%89%b6%e1%89%bd-%e1%88%9e%e1%89%b5-%e1%89%a0%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab/ Thu, 03 Feb 2022 08:54:02 +0000 https://yetenaweg.com/?p=2598 በሁስኒያ አደም (ጎንደር ዩ/ህ/ጤ/ሳ/ኮ የህክምና ተማሪ-C2)

A mother with her newborn child at Dessie Referral Hospital in Afar region, Ethiopia. Save the Children staff refer girls and women with health problems from rural Amhara to the hospital and assist them in their journey there.

በእያንዳንዱ ቀን ከ2 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማስቀረት በምንችላቸው ከእርግዝና እና ወሊድ ጋር በተያያዙ ምክንያቶች የሴት ልጅ ህይወት እንደሚያልፍ ያውቃሉን?

እ.ኤ.አ. በ2017 የተደረገ ጥናት እንደሚያሳየው 295,000 የሚሆኑ ሴቶች በእርግዝና እና ወሊድ ወቅት ህይወታቸው አልፏል። ከዚህም ውስጥ 94% የሚገኙት እያደጉ ባሉ ሀገራት ውስጥ ነው። ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሃገራት ውስጥ ብቻ 66% (196,000) የእናቶች ሞት ሲመዘገብ፣ ኢትዮጵያ 5% (14,000) ትይዛለች።

የእናቶች ሞት ማለት ምን ማለት ነው?

የእናቶች ሞት ማለት በእርግዝና ጊዜ ወይም ከወሊድ በኋላ በመጀመሪያ 42 ቀናቶች ውስጥ ከእርግዝናው ጋር ተያይዘው በሚመጡ የጤና ችግሮች ወይም በእርግዝናው ምክንያት ሊባባሱ በሚችሉ እና በህክምና አገልግሎት ችግር የሚከሰቱ የሴት ልጅ ሞት ማለት ነው።

በእርግዝና እና ወሊድ ጊዜ የሚከሰቱትን የጤና ችግሮች ለመቅረፍ የሚያስችሉ መፍትሄዎች በመኖራቸው አብዛኛውን የእናቶች ሞት መከላከል ይቻላል። በዋነኝነት ሁሉም የወሊድ አገልግሎት በትክክለኛ ጊዜ እንዲሁም ብቁ በሆኑ የጤና ባለሙያዎች መሰጠት አለበት። ይህም የአንድን እናት እንዲሁም የልጇን መኖር አለመኖር ይወስናል።

ለእናቶች ሞት የሚዳርጉ መንስኤዎች ምንድን ናቸው?

አብዛኛዎቹ የጤና ችግሮች በእርግዝና ወቅት የሚመጡ ሲሆኑ የቀሩት ከእርግዝና በፊት በነበሩ የጤና ችግሮች በእርግዝናው ምክንያት በመባባሳቸው የሚመጡ ናቸው።

ከባድ የደም መፍሰስ (በአብዛኛው ከወሊድ በኋላ የሚፈሰው ደም) ፣ በእርግዝና ወቅት የደም ግፊት መጨመር (pre-eclampsia and eclampsia) ፣ ኢንፌክሽን (sepsis) ፣ ከባድ ምጥ (Obstructed labour) እንዲሁም ከጤና ተቋም ውጪ ፣ ብቁ ባልሆኑ ባለሙያዎች እና በህክምና መሳርያ ያልታገዘ ውርጃ (Unsafe abortion) ለእናቶች ህይወት ማለፍ ዋነኛ መንስኤ ተደርገው ይወሰዳሉ።

የህክምና አገልግሎትን ለማግኘት ውሳኔን ማዘግየት ፣ ወደ ህክምና ተቋም ለመድረስ መዘግየት እና የጤና ተቋም ከደረሱ በኋላ አስፈላጊውን የህክምና አገልግሎት ሳያገኙ መዘግየት የእናቶችን ሞት የሚያስከትሉ ሶስቱ የመዘግየት ሞዴል (The Three Delays Model) በመባል ይታወቃሉ።

የእናቶች ሞት መጠን በእናቶች የእድሜ ክልል ይለያያል። በ 10 – 14 እድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ወጣት ልጃገረዶች በእርግዝና እና ወሊድ ምክንያት ከሌሎች የእድሜ ክልሎች በበለጠ ለሞት ይዳረጋሉ።

የእናቶችን ሞት እንዴት ማስቀረት እንችላለን?

. የአለም ጤና ድርጅት እንደሚያመለክተው የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎት የእናቶችን ሞት በመቀነስ ዙሪያ ጉልህ ሚና ይጫወታል። ይህም ያልተፈለገ እርግዝናን በማስቀረት ከእርግዝና  እና      ውርጃ ጋር ተያይዞ የሚከሰተውን የእናቶችን ሞት ይቀንሳል። የአፍላ እድሜን እርግዝና በማዘግየት የወጣት ልጃገረድን ህይወት ይታደጋል። በተጨማሪም የልጆቻቸውን ቁጥር፣ መች እና     በምን ያህል ርቀት እንደሚወልዱ ለማቀድ ያስችላል።

. የቅድመ ወሊድ ክትትል አገልግሎት ጤናማ የእርግዝና ጊዜን ለማሳለፍ ሌላኛው መፍትሄ ነው።

. የቅድመ ወሊድ ክትትል አገልግሎት ብቻውን በቂ አይሆንም። የእናቶችን ሞት ለመቀነስ ጤናማ የእርግዝና ጊዜ ማሳለፍ አስፈላጊ እንደሆነ ሁሉ በወሊድ ወቅትም በጤና ተቋም ብቁ ባለሙያ ባለበት መሆኑ አስፈላጊ ነው።

በሀገራችንም ባለፉት 15 አመታት ውስጥ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎት የሚጠቀሙ እናቶች መጠን በ27% ፣ የቅድመ ወሊድ ክትትል ያላቸው በ56% እንዲሁም በጤና ተቋም የወሊድ አገልግሎት ያገኙ በ22% መሻሻል አሳይቷል።

ከ1990 – 2015 የእናቶች ሞት መጠን ለውጥ ቢያሳይም አጥጋቢ አልነበረም። ውጤቱም ኢትዮጵያ ከምዕተ አመቱ የልማት ግቦች (MDGs) ጋር በተያያዘ ከታቀደው በታች መሆኑን ያሳያል።

በ2030ም EPMM (Ending Preventable Maternal Mortality) በእያንዳንዱ ሀገራት የሚከሰተውን የእናቶችን ሞት ቢያንስ በሁለት ሶስተኛ (2010ን መነሻ በማድረግ) ለመቀነስ ግብ አስቀምጧል።

 

ማጣቀሻ

  1. Ethiopian Public Health Institute (EPHI) and ICF. 2021. Ethiopia Mini Demographic and Health Survey 2019: Final Report. Rockville, Maryland, USA: EPHI and ICF.
  2. Organization WH. 2015. Strategies towards ending preventable maternal mortality (EPMM).
  3. Organization WH. 2019. Trends in maternal mortality 2000 to 2017: estimates by WHO, UNICEF, UNFPA, World Bank Group and the United Nations Population Division.
  4. Say L, Chou D, Gemmill A, Tunçalp Ö, Moller A-B, Daniels J, et al. 2014. Global causes of maternal death: a WHO systematic analysis. The Lancet global health. 2(6):e323-e33.
  5. Tessema GA, Laurence CO, Melaku YA, Misganaw A, Woldie SA, Hiruye A, et al. 2017. Trends and causes of maternal mortality in Ethiopia during 1990–2013: findings from the Global Burden of Diseases study 2013. BMC public health. 17(1):1-8.

ይህ ፅሁፍ በዶ/ር ዳዊት ወርቁ (የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስ/የማህፀን ካንሰር ሰብ ስፔሻሊስት) እና የጤና ወግ ኤዲተሮች የተገመገመ ነው።

 

]]>
የማህፀን ጫፍ ካንሰር በኢትዮጵያ https://srhr.yetenaweg.com/%e1%8b%a8%e1%88%9b%e1%88%85%e1%8d%80%e1%8a%95-%e1%8c%ab%e1%8d%8d-%e1%8a%ab%e1%8a%95%e1%88%b0%e1%88%ad-%e1%89%a0%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab/ Thu, 13 Jan 2022 14:44:21 +0000 https://yetenaweg.com/?p=2470 በቤቴልሄም መኮነን (በጎንደር ዩኒቨርሲቲ /// የህክምና ተማሪ-C2)

አብዛኞቻችን ካንሰር የሚለውን ስም በሀገራችን መስማት ከጀመርን ሩቅ አይደለም፡፡ በተለይም በገጠሩ የሀገራችን ማህበረሰብ ዘንድ ገና በመታወቅ ላይ ያለ ህመም ነው፡፡ በዚህም የተነሳ መታከም እንደሚችል ከማሰብ ይልቅ የፈጣሪ ቁጣ እንደሆነ የሚያስቡም በርካቶች ናቸው፡፡

በሀገራችን በርካታ ጥናቶች ባይደረጉም፣ ካንሰር 5.8 ከመቶ አመታዊ የሞት ምጣኔ እንዳለው ይገመታል፡፡ በስፋት ተሰራጭተው ከሚገኙት መካከል የጡት ካንሰር 30.2ከመቶ የሚሆነውን ድርሻ ሲይዝ የማህፀን ጫፍ ካንሰር 13.4ከመቶ እንዲሁም የትልቁ አንጀት ካንሰር 6.3ከመቶ የሚሆነውን ድርሻ በመያዝ ተቀምጧል፡፡

የማህፀን ጫፍ ካንሰር በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ ሌሎች ካንሰሮች በ4ኛ ደረጃ ላይ ይቀመጣል፡፡ እንደ የአለም ጤና ጥበቃ ድርጅት ጥናት መሰረት በ2020 በመላው ዓለም ከ604,000 በላይ ሴቶች በዚህ ካንሰር የተጠቁ ሲሆኑ ከ342,000 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ለሞት ተዳርገዋል፡፡ በኢትዮጵያም ከ6,294 የካንሰሩ ተጠቂዎች 4,884 የሞት ሰለባዎች ሆነዋል፡፡

በ2019 የተደረገው የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጥናት እንደሚያሳየው ከሆነ አብዛኞቹ የካንሰሩ ተጠቂዎች ስለ ካንሰሩ ምንም እውቀት የሌላቸው ሲሆኑ ሲመረመሩም በስፋት ወደ ሰውነታቸው ከተሰራጨ በኋላ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የሚታየው የግንዛቤ ማነስ ትኩረት የሚሻ ነው፡፡

የማህፀን ጫፍ ካንሰር ምንድን ነው?

✓ መከላከል እንደሚቻል እንዲሁም ቢታከም መዳን እንደሚችል ያውቃሉ ?

✓ ይህ ካንሰር ማህፀን በር አካባቢ ያሉ ህዋሶቻችን ከመጠን በላይ ሲራቡ የሚፈጠር እጢ ነው፡፡

✓ ከሞላጎደል ሁሉም(99%) የማህፀን ጫፍ ካንሰሮች ሂውማን ፓፒሎማ ቫይረስ (Human Papilloma Virus) በተሰኘ የቫይረስ ኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰቱ ናቸው፡፡ ይህ ቫይረስ የግብረ-ስጋ ግንኙነት በማድረግ የሚተላለፍ ነው፡፡ አንዲት ሴት በዚህ ቫይረስ (HPV) ብትጠቃም፣ ቫይረሱ በራሱ ጊዜ የመዳን እድል አለው በተለይም ከ90ከመቶ በላይ በ2ዓመት ይድናል፡፡

በምን ምክንያት ወደ ካንሰር ሊለወጥ ይችላል?

➢ አንዲት ሴት ከ16 ዓመቷ በፊት ወሲብ መፈፀም ከጀመረች አልያም ደግሞ የወር አበባ ማየት በጀመረችበት ዓመት ወሲብ ከፈፀመች

➢ ከአንድ በላይ የወሲብ ጓደኞች ከነበሯት

➢ የሚዋጥ የወሊድ መቆጣጠሪያ የምትጠቀም ከሆነ በተለይም ለ5 ዓመትና ከዚያ በላይ ➢ ሲጋራ የምታጨስ ከሆነ

➢ የተዳከመ በሽታን የመቋቋም አቅም ካላት

➢ የምግብ ዕጥረት ለምሳሌ እንደ ቫይታሚን ቢ፣ሲ፣ኢ የመሳሰሉት

➢ በአባላዘር በሽታዎች ከተጠቃች

➢ የቅድመ የማህፀን ጫፍ ካንሰር ምርመራ አድርጋ የማታውቅ ከሆነ

➢ ዝቅተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ

ምልክቶቹ ምንድናቸው?

ከሆነ በአስቸካይ በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ የሀኪም እርዳታ ማግኘት ያስፈልጋል፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ ካንሰር ምንም ምልክት ላያሳይ ይችላል ወይም ደግሞ መጠነኛ ምልክቶች ብቻ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ስለሆነም መዘናጋት ተገቢ አይደለም፡፡

የማህፀን ጫፍ ካንሰርን እንዴት እንከላከል?

ቅድመ መከላከል

ለታዳጊ ሴቶች ማለትም ከ9-14ዓመት ለሆኑ

➢ የሂውማን ፓፒሎማ ቫይረስ(HPV) ክትባት መስጠት

➢ በሀገራችንም እ.ኤ.አ ከ2018 ጀምሮ ከ14 ዓመት በላይ ለሆኑ ታዳጊዎች በየትምህርት ቤቱ እንዲሁም በጤና ተቋማት የሂውማን ፓፒሎማ ቫይረስ(HPV) ክትባት መሰጠት ተጀምራል፡፡ይህ ተግባር ሁሉንም ዜጋ ተደራሽ በማድረግ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡

ለሴቶችና ለወንዶች

➢ እድሜና ባህልን መሰረት ያደረገ የጾታዊ ግንኙነት ትምህርት መስጠት

➢ ወሲብ መፈፀም ለጀመሩ ኮንዶምን እንዲጠቀሙ ማበረታታት

➢ የወንዶች ግርዛት

➢ ስለ ሲጋራ የጤና ጠንቆች ግንዛቤ መስጠት

2ኛ ደረጃ መከላከል

➢ 30ዓመትና ከዛ በላይ ለሆኑ ሴቶች የሚተገበር ሲሆን የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም የቅድመ ካንሰር ምርመራ ማድረግ ነው

3ኛ ደረጃ መከላከል

እንደአስፈላጊነቱ ለሁሉም ሴቶች ሲሆን በተለይም አደገኛ የሆኑትን የካንሰር ምልክቶች ማሳየት ለጀመሩ ሴቶች ተገቢውን ህክምና መስጠት ነው፡፡

አማራጮቹም ፡-

– የቀዶ ህክምና

– የጨረር ህክምና

– ኬሞቴራፒ

የአሜሪካ የካንሰር ማህበረሰብ፣ የማህፀን ጫፍ ካንሰር ቅድመ ምርመራን በተመለከተ መቼ መጀመር እንዳበትና መች እንደሚቋረጥ የሚከተለውን ያስቀምጣል ፡

– አንዲት ሴት ወሲብ መፈፀም ከጀመረች ከ3ዓመት በኋላ፤ ከ21ዓመት ባይበልጥ ይመከራል

– እንደአስፈላጊነቱ በየ2 ወይም በ3 ዓመት ልዩነት መደገም አለበት፡፡ ይሁንእንጂ እንደ ኤች.አይ.ቪና ሌሎች በሽታን የመቋቋም አቅምን የሚያዳክሙ ሁኔታዎች ካሉ በየአመቱ መደገም እንዳለበት ተቀምጧል፡፡

– አንዲት ሴት ላለፉት 10ዓመታት ምንም አስጊ ሁኔታ ላይ ካልሆነች ከ70 ዓመቷ በኋላ የቅድመ ምርመራውን ማቋረጥ ትችላለች

ዋቢ

  1. Saleem A, Bekele A, Fitzpatrick MB, Mahmoud EA, Lin AW, Velasco HE, et al. Knowledge and awareness of cervical cancer in Southwestern Ethiopia is lacking: A descriptive analysis. PLoS One. 2019;14(11):e0215117.
  2. Begoihn M, Mathewos A, Aynalem A, Wondemagegnehu T, Moelle U, Gizaw M, et al. 2019. Cervical cancer in Ethiopia–predictors of advanced stage and prolonged time to diagnosis. Infectious agents and cancer, 14(1):1-7.
  3. world health organization.2021. Cervical cancer. https://www.who.int/health-topics/cervical cancer#tab=tab_1
  4. world health organization.2021. cervical cancer elimination initiatives. https://www.who.int/initiatives/cervical-cancer-elimination-initiative

 

ይህ ፅሁፍ በዶ/ር ዳዊት ወርቁ (የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት/የማህፀን ካንሰር ልዩ ስፔሻሊስት) እና የጤና ወግ ኤዲተሮች የተገመገመ ነው።

]]>
የምጥ መሠናከል (Obstructed Labor) https://srhr.yetenaweg.com/%e1%8b%a8%e1%88%9d%e1%8c%a5-%e1%88%98%e1%88%a0%e1%8a%93%e1%8a%a8%e1%88%8d-obstructed-labor/ Sun, 20 Sep 2020 21:17:31 +0000 http://yetenaweg.home.blog/?p=1434 Mewael Girma, (Medical student – Clinical Year One ) –Arsi University, Assela Referral and Teaching Hospital

የምጥ መሠናከል (Obstructed Labor)

በሀገራችን አዘውትረን ከምንሰማቸው የእናቶች ስቃይ እና ሞት ምክንያት አንዱና ዋነኛው በወሊድ ወቅት የሚፈጠር ችግር ሲሆን ለዚህም በምክንያትነት ከሚጠቀሱት አንዱ እስከ ቀናት የሚደርስ የምጥ ጊዜ መርዘም ነው፡፡ ለምጥ መርዘም ደግሞ የምጥ መሠናከል  በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡

አብዛኛውን ጊዜ የሚከሰተው ያላደጉ እና አዳጊ ሃገራት ላይ ሲሆን ከአጠቃላይ ወሊዶች እስከ 8% የሚደርሱት የምጥ መሠናከል ያጋጥማቸዋል፡፡

የምጥ መሠናከል ምንድን ነው? 

መሠረታዊ ሀሣቡን በቀላሉ ለመረዳት የሚወለደው ፅንስ እና የሚያልፍበት የማህፀን ክፍል አካላዊ አለመመጣጠን ሲከሰት የምጥ መሠናከል እንለዋለን፡፡ ተገቢውን መፍትሔ እስኪያገኝ ድረስም የምጥ ጊዜ መራዘምን ያመጣል፡፡

አንድ የተረገዘ ፅንስ ሲወለድ በምጥ ወቅት የሚከተሉት ሁኔታዎች በተያያዘ መልክ የውልደት ሂደቱን ያሳኩታል፡

1– በቂ የሆነ የማህፀን መኮማተር እና በምጥ ወቅት እናት ፅንሱን የምትገፋበት ሃይል

2– የተገፋው ፅንስ የሚያልፍበት ምቹ የማህፀን ክፍል፣ የዳሌ አጥንት እና በዙሪያው የሚገኙ አካላት

3– የፅንሱ ስፋት፣ ክብደት፣ ተፈጥሯዊ ቅርፅ፣ የማህፀን ውስጥ አቀማመጥ እና አቀራረብ 

በተሰናከለ ምጥ ወቅት ከላይ ከተጠቀሱት ውስጥ (1) በበቂ ሁኔታ እያለ (2) ወይም (3) ላይ በተናጠል ወይም ተደራራቢ የሆኑ የተለያዩ እክሎችን እናገኛለን፡፡ ይህም ማለት ለውልደቱ እንቅፋት የሆነው የማህፀን መኮማተር እና ግፊት ሣይሆን በፅንስ እና ማህፀን ላይ የሚኖሩ አካላዊ አለመመጣጠኖች ናቸው፡፡

ምክንያቶቹስ?

ቀጥተኛ፡ በእናት እና ፅንስ ላይ ያሉትን ቀጥተኛ እክሎች በምክንያትነት ለማየት ለሁለት እንከፍላቸዋልን፡ የእናት አካላዊ እክሎች እና የፅንስ አካላዊ እክሎች

የእናት አካላዊ እክሎች

  • ያልተለመደ ቅርፅ ያለው ወይም ጠባብ የዳሌ አጥንት
  • የዳሌ አጥንት እጢዎች
  • በማህፀን እና ተያያዥ አካላት ላይ የሚወጡ እጢዎች
  • የማህፀን ወይም ተያያዥ አካላት ተፈጥሯዊ ቅርፅ መዛባት

የፅንስ አካላዊ እክሎች

  • በማህፀን ውስጥ አመቺ ያልሆነ አቀማመጥ እና አቀራረብ
  • መጠን ያለፈ ክብደት እና ስፋት
  • ሁለት (መንታ) እና ከዚያ በላይ ፅንስ
  • የተቆላለፉ ወይም የተጣበቁ መንታዎች
  • ተፈጥሯዊ ወይም በሽታን ተከትሎ የሚመጣ ቅርፅ መዛባት

 

ተዘዋዋሪ፡

አብዛኛው ህብረተሰባችን ውስጥ ያለው የገንዘብ እጥረት፣ የግንዛቤ አለመኖር እና ወደ ጤና ማዕከል ለመሔድ የሚጠቅሙ የትራንስፖርት እና የመንገድ ችግር አሁን ካለን ሁሉን ያላዳረሰ የጤና ሥርዓት ጋር በመደመር እናቶች በእርግዝና እና በወሊድ ወቅት ተገቢውን ሕክምና እንዳያገኙ በማድረግ እንደ ምጥ መሠናከል ላሉ እና ተከትለው ለሚመጡ የጤና እክሎች ምክንያት ይሆናሉ፡፡

የምጥ መሠናከል ምልክቶች

  • 24 ሠዓት ያለፈ ረጅም ምጥ
  • የሽል ውሃ መፍሰስን ተከትሎ የምጥ መዘግየት
  • ከማህፀን የሚወጣ መጥፎ ሽታ ያለው ፈሳሽ
  • ቶሎ ቶሎ እየመጣ የሚጠፋ ጠንካራ ምጥ
  • ምጥን ተከትሎ የሚመጣ የማህፀን ደም መፍሰስ
  • ትኩሳት፣ ፍፁም ድካም ፣ የህመም ስሜት እና የእንቅልፍ እጦት

የምጥ መሠናከል ለምን ይዳርጋል?

ተገቢውን ክትትል እና ህክምና ካገኘ በቀላሉ መፍትሔ ማግኘት የሚችል እክል ነው፡፡ ነገር ግን ያለ ህክምና እናትንም የሚወለደውንም ፅንስ እስከሞት ለሚያደርሱ የተለያዩ  ሁኔታዎች ይዳርጋል፡፡ እነሡንም ለሁለት ከፍለን እናያለን፡ እናት እና ፅንስ ላይ፡

እናት

  • ኢንፌክሽን
  • ድህረ-ወሊድ ደም መፍሰስ እና ደም ማነስ
  • የመራቢያ አካላት እና የሽንት ፊኛ መጎዳት
  • የነርቭ በሽታ
  • የማህፀን ግድግዳ መሰንጠቅ
  • መሃንነት
  • ፊስቱላ (ሽንትና ሠገራን አለመቆጣጠር)
  • ሥነልቦናዊ ጉዳት

ፅንስ

  • መታፈን
  • ኢንፌክሽን
  • ጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ
  • የነርቭ በሽታ
  • አካል ጉዳት

የምጥ መሠናከል ለማስወገድ የሚደረጉ ቅድመ-ጥንቃቄዎች እና መፍትሔዎቹ

  • ተገቢውን የቅድመ-ወሊድ፣ ወሊድ እና ድህረ-ወሊድ ክትትል በጤና ተቋም ማድረግ
  • የቤት ውስጥ ወሊድን ማስቀረት
  • በቂ የሆነ ዕውቀት እና ልምድ ወደሌላቸው አዋላጆች አለመሄድ
  • የስነ-ተዋልዶ ዕውቀት እና ግንዛቤን መፍጠር (የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች፣ ያለዕድሜ ጋብቻ…)
  • ሴት ልጆች አድገው ለዚህ አካላዊ እክል እንዳይዳረጉ የተመጣጠነ ምግብ መስጠት
  • የጤና ተቋማትን በበቂ ሁኔታ ማዳረስ እና የትራንስፖርት እና የመንገድ ችግሮችን መቅረፍ

የምጥ መሠናከልን ለማስወገድ የተጠቀሱትን ቅድመ-ጥንቃቄዎች ካደረግን እንዲሁም ተገቢውን ምክር እና ክብካቤ ከተገቢ እና ብቁ የጤና ባለሙያ ካገኘን እና ከተገበርን የተሳካ የወሊድ ሂደት እናገኛለን፡፡ ሳይሆን ቀርቶም ተያያዥ የሆኑ እክሎች ካጋጠሙን ጊዜ ሳንፈጅ አቅራቢያ በሚገኝ ጤና ተቋም በመሄድ ከቀላል ክትትል እስከ መፍትሔ ሠጪ ቀዶ ጥገና፣ ተገቢ ህክምና በተጨማሪም ለቀጣይ እርግዝና በቂ ግንዛቤ ማግኘት እንችላለን፡፡ 

ዋቢ / REFERENCES

  1. OBSTETRICS: NORMAL AND PROBLEM PREGNANCY, 7TH Edition, 2019
  2. CURRENT DIAGNOSIS TREATMENT OBSTETRICS AND GYNECOLOGY, 11TH Edition, 2013
  3. UpToDate 21.6
  4. AYDER’S OBSTETRIC AND GYNECOLOGY, 1ST Edition, 2020

MANAGEMENT PROTOCOL ON SELECTED OBSTETRIC TOPICS, FMOH, 2010 E.C.

 

ይሄ  አስተማሪ  የህክምና ፅሁፍ የቀረበው  የጤና ወግ እና የ ኢትዮጵያ ሕክምና ተማሪዎች ማህበር ባዘጋጁት የህክምና ተማሪዎችን የመረጃ አስበሰብ እና ህብረተሰቡን የማስተማር አቅማቸውን ለማዳበር ለታለመ የበጎ ፍቃድ ውድድር ነው። እያንዳንዱ ፅሁፍ በ ጤና ወግ የታየ እና እርማት ተደርጎበት የቀረበ ነው ።

]]>
የጡት ካንሰር https://srhr.yetenaweg.com/%e1%8b%a8%e1%8c%a1%e1%89%b5-%e1%8a%ab%e1%8a%95%e1%88%b0%e1%88%ad-2/ Wed, 02 Sep 2020 02:43:08 +0000 http://yetenaweg.home.blog/?p=1301 በ ፍስሀ ሙሉጌታ (2nd Year Medical Student- Myungsung Medical College)

1.1 መግብያ 

ዕጢ(Tumor) ማለት የሕዋሳት ስብስብ ማለት ነው ፡፡ ይህ ማለት ጤናማ ያልሆነ (በአጠቃላይ ጉዳት 

የሌለው) ወይም አደገኛ (ካንሰር) እድገትን ሊያመለክት የሚችል አጠቃላይ ቃል ነው ፡፡ 

የጡት ካንሰር ማለት በጡት ሕብረ ሕዋሳት ውስጥ የህዋሳት ቁጥር በማያስፈልግ መጠን እና ሁኔታ 

መራባት ነው ፡፡ ባደጉት ሀገራት ውስጥ ከ 2/3 ኛ በላይ የጡት ካንሰር ከ50 እና ከዚያ በላይ ዕድሜ የሆኑ ሴቶችን  ይጠቃል ። በተቃራኒው ኢትዮጵያ ውስጥ በተሰ ራ ጥናት ከ 70% በላይ የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ዕድሜያቸው ከ 50 ዓመት በታች መሆኑን በጥናት ታይቷል  ፡፡ የሱዳን (74%) ፣ ሊቢያ (71%) ፣ እና ጋና (54.2%) ከ50 አመት በታች ነው። 

የጡት ካንሰር በዓለም ዙሪያ ላሉ ሴቶች ለእጅግ በጣም ብዙ ህመም እና  ሞት ምክንያት ነው፡፡ የተለያዩ ሰዎች የተለያዩ የጡት ካንሰር ምልክቶች ያሳያሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች በሽታው እስኪፋፋ ድረስ  በጭራሽ ምንም ምልክቶች ላያሳዩ ይችላሉ  ፡፡  

በጡት ካንሰር ብዙ ጊዜ ሴቶች ቢጠቁም ወንዶችም አንዳንድ ጊዜ በበሽታው ሊያዙ ይችላሉ። 

1.2 የጡት ካንሰር ምልክቶች 

• በጡት ውስጥ ወይም ብብት ስር እብጠት፡፡ 

• የጡት የተወሰነ ክፍል ውፍረት ወይም እብጠት። 

• በጡት ጫፍ አካባቢ ህመም ፡፡ 

• በእርግዝና እና በማጥባት ወቅት ካልሆነ በስተቀር ከ ጡት ጫፍ የሚታይ ፍሳሽ (ደምን ጨምሮ) ።

• በአንዱ ወይም በሁለቱም የጡት ጫፎች መልክ (ቅርፅ) ለውጦች ፡፡ 

• የ ጡት ቀለም  መለወጥ፡፡ 

• በአጭር ጊዜ ውስጥ የጡት መጠን ወይም ቅርፅ መጨመር 

• የጡት ጫፍ ቆዳ መጎጥጎጥ  ወይም ወደ ውስጥ መግባት 

• የጡት ቆዳ መቅላት ወይም መላጥ (ልክ እንደ ብርቱካን ቆዳ) 

እንደነዚህ ያሉትን ምልክቶች ካዩ በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ ሆስፒታል ይጎብኙ፡፡ 

1.3 በጡት ካንሰር የመያዝ መንስኤ (Risk factors) 

የሚከተሉት የጡት ካንሰርን የመያዝ እድልን ይጨምራሉ፡- 

•ሴቶች- የጡት ካንስር በአብዛኛውን ጊዜ ሴቶችን ያጠቃል።  ግን ወንዶችንም በበሽታው ሊያዙ ይችላሉ።

•እድሜ፡- የጡት ካንሰር የመያዝ እድል ከእድሜ ጋር ይጨምራል ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የጡት ካንሰር

ከ 50 ዓመት እድሜ በኋላ ይመጣል። 

•አንዳድ በዘር ውስጥ የሚመጡ የዘረመል ለውጦች (ሚውቴሽን) ፡-እነዚህን የዘር ለውጦች የወረሱ ሴቶች በከፍተኛ መልኩ የጡት እና የማህጸን ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከፍተኛ ነው ፡፡ 

ከወለዱ በኋላ ጡት አለማጥባት፡፡ 

ከ 12 ዓመት እድሜ በፊት የወር አበባ መምጣት እና ከ 55 ዓመት እድሜ በኋላ የወር አበባ ዘግየቶ መቆም ሴቶችን በሆርሞኖች ረዘም ላለ ጊዜ ያጋልጣሉ፡፡ ይህም የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድልን  ከፍ 

ያደርገዋል ፡፡ 

ጥቅጥቅ ወይም ወፋፍራም ያሉ ጡቶች ካሉዎት ፡፡ ጥቅጥቅ ያሉ ጡቶች ብዙ ሕብረ ሕዋሳት አላቸው ፣ ይሄም በጡት ካንሰር የመጋለጥ እድላችንን ከፍ ያደርገዋል። በተጨማሪም ከእንደዚህ አይነት ጡቶች አንዳንድ ጊዜ ዕጢዎችን በማሞግራም ላይ ማየት ከባድ ያደርገዋል ፡፡ 

የጡት ካንሰር ከዚህ በፊት የተያዙ ወይም የተወሰኑ ካንሰር ያልሆኑ የጡት በሽታዎች ያጋጠማቸው ሴቶች ለሁለተኛ ጊዜ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡ 

የጡት ካንሰር የቤተሰብ ታሪክ፡- የመጀመሪያ-ደረጃ ዘመድ (አባት፣ እናት ፣ ወንድም፣ እህት ወይም ልጅ) 

በጡት ካንሰር ተይዘው የሚያውቁ ከሆነ በጡት ካንሰር የመያዝ ዕድሎ ይጨምራል፡፡ 

ከ 30 ዓመት ዕድሜ በፊት በደረት ላይ ወይም በጡት ላይ የጨረር ሕክምና የነበራቸው (እንደ ሆጅኪ ንስ ሊምፎማ ሕክምና ያሉ) በጡት ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከፍተኛ ነው ፡፡ 

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እጥረት እና ከአቅም በላይ ውፍረት። 

ሆርሞኖችን መውሰድ– የወር አበባ ከቆመ በኋላ የሚወሰዱ ሆርሞኖች (ኤስትሮጅንና ፕሮጄስትሮን 

የተባሉትን) ከአምስት ዓመት በላይ ሲወሰድ ለጡት ካንሰር የመያዝ እድልን ከፍ ያደርጋሉ ፡፡ 

የመጀመሪያ እርግዝና ከ 30 ዓመት እድሜ በኋላ ከሆነ  እና ሙሉ ጊዜ(9 ወር) ሳይጨርሱ መውለድ የጡት  ካንሰርን የመያዝ ዕድልን ከፍ ሊያደርጉ ይችላሉ ፡፡ 

አልኮል መጠጣት፡- ጥናቶች እንደሚያመለክቱት አንዲት ሴት ለጡት ካንሰር የመጋለጥ እድሏ 

በምጠጣው አልኮል መጠጥ መጠን ይጨምራል ፡፡ 

አንዳንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ መድሀኒት የጡት ካንሰርን የመያዝ እድልን ከፍ ያደርጋል ይላሉ ነገር ግን 

የመውለድ እድሜያቸው ያላበቃ ሴቶችን አያጠቃልልም፡፡ ተጨማሪ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት በአፍ 

የሚወሰድ የወሊድ መከላከያ የማህፀን ካንሰር የመያዝ እድልን ይቀንሳል ፡፡ 

በ ጡት ካንሰር የተያዘ የመጀመሪያ ደረጃ ዘመድ(አባት፣ እናት ፣ ወንድም፣ እህት ወይም ልጅ)  ካለዎት  ወይም በዚህ ጽሑፍ ላይ ከተዘረዘሩት ምልክቶች መካከል አንዱን ወይም ከዚያ በላይ ከተመለከቱ ሃኪምዎ  ጋር ይሂዱ፡፡

እነዚህ ምልክቶች ሲኖሩዎት የጡት ካንሰር አለብዎት ማለት አይደለም ነገር ግን ወደ ሐኪም በመሄድ ማረጋገጥ ያስፈልጋል ፡፡ 

1.4 የጡት ካንሰር ምርመራ 

ማሞግራም የጡት ራጅ(x-ray) ነው ፡፡ማሞግራም ምንም ምልክት በሌላቸው ሰዎች ውስጥ በሽታን 

ለማግኘት የሚያገለግል መሳርያ ነው፡፡ በአሜሪካ ካንሰር ማህበረሰብ መሠረት “ከ 40 እስከ 44 ዓመት 

ዕድሜ ያላቸው ሴቶች አመታዊ የማሞግራም ምርመራ ማድረግ ይችላሉ (ግዴታ አይደለም)፡፡ ከ 45 እስከ 

54 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴቶች ግን በየአመቱ ማሞግራም መነሳት አለባቸው ፡፡ ዕድሜያቸው ከ 55 

ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሴቶች በየ2 ዓመቱ ማሞሞግራም መነሳት አለባቸው ወይም በየዓመቱ 

ምርመራውን የመቀጠል ምርጫ አላቸው ፡፡ 

ክሊኒካዊ ( በአካላዊ ምርመራ እና ክትትል ብቻ ) -ማሞግራም መሳርያን ባለመጠቀም  የጡት 

ምርመራ በማንኛውም ዕድሜ ላይ ላሉ እና በአማካኝ ተጋላጭ ናቸው ተብለው ለሚታስቡ ሴቶች የጡት 

ካንሰርን ምርመራ ለማካሄድ አይመከርም፡፡”  ምንጭ American Cancer Society

1.5 የወንድ የጡት ካንሰር 

የወንድ የጡት ካንሰር እንደ ሴቶች የተለመደ ስላልሆነ በሽታው ከፍ ያለ ደረጃ እስኪደርስ ላይታወቅ ይችላል ። በዚያን ጊዜ ካንሰር ቀድሞውኑ ተሰራጭቶ ሊሆን ይችላል ፡፡ ስለዚህ ይህንን ጽሑፍ የሚያነቡ ወንዶች በጡት ጫፍ ወይም በጡት አካባቢ እብጠት ቢያገኙ እና በዚህ ጽሑፍ ላይ የተጻፉ ሌሎች 

ምልክቶችንም ቢመለከቱ ወዲያውኑ ወደ ሐኪም ሄዶ ምርመራውን እንዲያካሂዱ ይመከራል ፡፡ 

1.6 የጡት ካንሰር ሕክምና 

ለጡት ካንሰር ሕክምናዎች ዋነኞቹ ሕክምናዎች በካንሰር ደረጃ ላይ በመመርኮዝ የቀዶ ጥገና ፣ ኬሞቴራፒ 

፣ ሆርሞናዊ ቴራፒ እና ራዲዮቴራፒ ናቸው ፡፡ የቀዶ ጥገናው ካንሰሩን ሙሉ በሙሉ ማውጣት ወይም ሙሉውን ጡት መቆረጥ ሊያካትት ይችላል። ከዚያ በኋላ  አንዳንድ ሰዎች ተጨማሪ ኬሞ እና ራዲዮቴራፒ ያስፈልጋቸዋል ፡፡ 

የኬሞቴራፒ ሕክምናው እንደ ጡት ካንሰሩ አይነት እና ደረጃ የሚወሰን ነው። የኬሞቴራፒ መድኃኒቶች የበሽታውን መስፋፍት የሚከላከሉ እና ተመልሶ እንዳይመጣ የሚያረጉ መድኃኒቶች ሲሆኑ እንደ አይነታቸው የተለያዩ የጎንዮሽ ጉዳቶች አላቸው። ሕክምናውን ከመጀምርዎ በፊት ሐኪምዎ የመድሃንቶቹን አወሳሰድ ፣ ጥቅም እና የሚያስከትሉትን ጉዳቶች ዘርዝሮ ያስረዳዎታል። 

1.7 ማጠቃለያ 

የጡት ካንሰር በዓለም ላይ በ ብዛት ከሚከሰቱ እና ሴቶች ላይ ሞትን ከሚያስከትሉ ህመሞች አንዱ ነው።  በሽታውን አስቀድሞ  ለመከላከል እና ከታወቀም በኃላ የሚያመጣውን ጉዳት ለመቀነስ ስለ ህመሙ ማወቅና እና መረዳት ያስፈልጋል ።

 ኢትዮጵያ እያደገች ስትመጣ ይህንን በሽታ በበቂ ሁኔታ ለማከም በሁሉም ክልሎች ውስጥ 

ማዕከላት ይኖራሉ የሚል እምነት አለኝ ፡፡ ነገር ግን እስከዛ ድረስ እራሳችንን ከበሽታው እንጠብቅ፡፡ ጡት 

በማጥባት፣ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ክብደታችንን በመቆጣጠር ፣ ተገቢ የሆነ መደበኛ የ ሕክምና ክትትል በማድረግ ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡንን ጠንቆች በተወሰነ መልኩ መቀነስ እንችላለን።

Reviewed and Edited by Yetenaweg

]]>
ከእርግዝና ጋር ተያይዞ የሚመጣ የደም ግፊት መጨመር (ፕሪኤክላምሲያ ) https://srhr.yetenaweg.com/%e1%8a%a8%e1%8a%a5%e1%88%ad%e1%8c%8d%e1%8b%9d%e1%8a%93-%e1%8c%8b%e1%88%ad-%e1%89%b0%e1%8b%ab%e1%8b%ad%e1%8b%9e-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%88%98%e1%8c%a3-%e1%8b%a8%e1%8b%b0%e1%88%9d-%e1%8c%8d%e1%8d%8a/ Tue, 01 Sep 2020 04:24:59 +0000 http://yetenaweg.home.blog/?p=1292 By. Elsa Wolde ( Medical Student- Clinical year three-AAU)

  ከእርግዝና ጋር ተያይዞ የሚመጣ የደም ግፊት መጨመር ወይም በእንግሊዘኛው ፕሪኤክላምሲያ  በእርግዝና እና በወሊድ ወቅት ለሚከሰቱ የእናቶች እና የልጆች ስቃይ እንዲሁም ሞት  ዋና ምክንያቶች ከሆኑት መካከል የሚጠቀስ ነው።

    ፕሪኤክላምሲያ  ማለት እርግዝናው ቢያንስ ሀያ ሳምንት ከሞላው በኋላ የሚመጣ የደም ግፊት መጨመር  እና በሽንት ውስጥ ያለው የፕሮቲን መጠን ከበፊቱ ከፍ ሲል ማለት ነው። 

    በሽታው በማንኛውም እርግዝና ላይ ሊከሰት የሚችል ሲሆን ተጋላጭነትን ከሚጨምሩት መካከል:-

     እድሜ – ከ 20 አመት በታች ወይም ከ35 አመት በላይ

    –  የመጀመሪያ ጊዜ እርግዝና

     ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ልጆችን በአንድ ጊዜ ማርገዝ

     – አዲስ የግብረ ስጋ ግንኙነት ጋደኛ አጋር 

      ከዚህ በፊት የተጓዳኝ በሽታዎች መኖር: የስኳር በሽታ፣ የኩላሊት በሽታ፣ ከመጠን በላይ የሆነ ውፍረት፣ የደም ግፊት

    –   ከዚህ በፊት በሽታው የተጠቃ ሰው በቤተሰብ መሀል መኖር

ከዚህ በፊት በበሽታው መያዝ  

  – ከዚህ በፊት ያልተሳካ እርግዝና መኖር  ዋነኞቹ ናቸው።

ይህ በሽታ እንደ ልብ፣ ሳንባ፣ ኩላሊት፣ አእምሮ እና አይንን ሊያጠቃ ይችላል።

ምልክቶቹም

የበሽታው ደረጃ ቀላል ከሆነ ምንም አይነት ምልክቶች ላይታዩ ይችላሉ። ነገር ግን በሽታው በቀላሉ ሊባባስ የሚችል እና የእናት እና የልጅን ጤና ሊያስተጓጉል ባስ ካለም ለሞት ሊዳርግ የሚችል ነው።

ዋና ዋና ምልክቶቹም:            

    – ቋሚ የሆነ ወይም ከሌላ ጊዜው የባሰ የራስ ምታት

    –  እይታ ላይ ብዥ ማለት፣ ጊዜያዊ የሆነ የእይታ መጋረድ ወይም ብርሀን መጥላት 

    –  የላይኛው በቀኝ በኩል ያለው የሆድ ክፍል ህመም፣ 

    – ግራ የመጋባት ስሜት

    – አዲስ የሆነ  የትንፋሽ ማጠር ዋነኞቹ ናቸው።        

 በህክምና ማእከል ተገቢውን የእርግዝና ክትትል ማድረግ በሽታው በቀላሉ እንዲታወቅና ተገቢው እርምጃ በቀላሉ እንዲወሰድ ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።

 በተጨማሪም ደግሞ ከላይ የተጠቀሱትን ምልክቶች ሲታዩ የበሽታውን መባባስ የሚጠቁሙ በመሆናቸው  በአፋጣኝ ወደ የህክምና ማእከል በመሄድ እርዳታ ማግኘት አስፈላጊ ነው።

ምንጮች:

  • https://www.uptodate.com/contents/preeclampsia-clinical-features-and-diagnosis
  • Current Diagnosis & Treatment Obstetrics & Gynecology, 11th Edition

ይሄ አስተማሪ  የህክምና ፅሁፍ የቀረበው  የጤና ወግ እና የ ኢትዮጵያ ሕክምና ተማሪዎች ማህበር ባዘጋጁት የህክምና ተማሪዎችን የመረጃ አስበሰብ እና ህብረተሰቡን የማስተማር አቅማቸውን ለማዳበር ለታለመ የበጎ ፍቃድ ውድድር ነው። እያንዳንዱ ፅሁፍ በዘርፉ ባለሙያ ስፔሺያሊስት ሀኪም የታየ እና እርማት ተደርጎበት የቀረበ ነው ።

Reviewed by : Dr.Dawit Worku

]]>